Popular posts from this blog
ኢትዮጵያዊው የታሪክ ፍቅረኛ
ለዛሬ ይዤላችሁ የቀረብኩት ኢትዮጵያዊ ወግና ቁም ነገር ሁሌም ባወራለት ስለማይሰለቸኝ ሰው ነው። ኢትዮጵያ የታላላቅ ታሪኮች ባለቤት መሆኗን፣ የሰው ዘር መፈጠሪያ እንደሆነች ለመጀመሪያ ጊዜ ስላበሰረውና እንዲሁም ደግሞ በኢትዮጵያ ፍቅር ወድቆ ዜማውም፣ ብዕሩም፣ ቴአትሩም፣ ግጥሙም፣ መንፈሱም ኢትዮጵያ እንደሆነች በፍቅር ስለተለያት ባለቅኔው ሎሬት ፀጋዬ ገ / መድህን ይሆናል፡ - ኢትዮጵያ እና ሕዝቦችዋ በመድረክ ላይ ገዝፈው እንዲወጡ፣ በታሪክ ውስጥ ገናና ህዝቦች እንደሆነ ሲፅፍላቸው፣ የኢትዮጵያም አንድነት ከብረት በደደረ መልኩ እንዲጠነክር ለኢትዮጵያ ሰማዕት የሆኑ ባለታሪኮችን በምሳሌነት እያቀረበ ፀጋዬ ገ / መድህንት ብዙ የሰራ የዚህች ሀገር ባለቅኔ ነው። ፀጋዬ አፄ ቴዎድሮስ መቅደላ ላይ ሽጉጣቸውን መዝዘው ራሳቸውን ለኢትዮጵያ ሲሉ የሰውበትን ታሪክ በመመርኮዝ የንጉሡን ስብዕና ወደ ፍልስፍና ቀይሮታል። ይህም ፍልስፍና ቴዎድሮሳዊነት እንዲባል ያደረገበት ነው። ቴዎድሮሳዊነት ማለት ለሐገር ክብር፣ ለኢትዮጵያ ፍቅር ራስን መሰዋትን ይመለከታል። ፀጋዬ ቴዎድሮስ በተሰኘው ግዙፍ ቴአትሩ ያሳየው ይህን ፍልስፍና ነው። ከኢትዮጵያ በላይ ምንም ነገረ የለም በማለት ራስን መስጠት። የኢትዮጵያን ክፉ ከማይ እኔ በቅድሚያ ልሰዋ ማለትን በቴዎድሮስ በኩል አሳይቷል። አፄ ቴዎድሮስ ይህችን ኢትዮጵያ ብለን የምንጠራትን ሐገር አንድነቷ ተጠብቆ፣ አንዲት ታላቅ ሀገር የመመስረት ህልም እና ይሄን ህልም ዕውን ለማድ...
Comments
Post a Comment